WORSHIP
በብሉይ ኪዳን “ያመልከኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ” ብሎ እግዚአብሔር የተናገረውን፤ እንዲሁም ደግሞ በአዲስ ኪዳን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “..ነገር ግን በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አሁንም ሆኖአል፤ አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና። “ የሚለውን እውነት በመረዳት አምልኮ በ ኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ሕብረት ቤተ ክርስቲያን በሂውሰተን ትልቅና ክቡር ስፍራ አለው። በቤተ ክርስቲያናችን በሚገኙ “ሀ” ና “ለ” የመዘምራን አገልግሎትና በቅርቡም በተቋቋመው የአምልኮ ቡድን አማካይነት ሰፊ የአምልኮ አገልግሎት ይካሄዳል። በነዚህ የአምልኮ አገልግሎቶች ውስጥ ያሉ አባላት ቤተ ክርስቲያኒቱ በቋሚነት ከምትሰጠው ሳምንታዊ ፕሮግራሞች ሌላ በዓመቱ ውስጥ በሚካሄዱት ልዩ ልዩ ኮንፈረንሶች ላይ ትልቅ ተሳትፎ ያደርጋሉ። በዓለም ዚሪያ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ይህንን አገልግሎት ለሚሰጡ ሁሉ የእግዚአብሔር
ፀጋ ይብዛላችሁ እንላለን።
Featured worship video